Welcome to Nifas Silk Lafto Subcity Peace and Security Office!       እንኳን ወደ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       ጽ/ቤቱ ክ/ከተማችን በህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነት ሰላምና ጸጥታ የሰፈነባት፤ የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ለኑሮ፣ ለስራ እና ለመዝናኛ ተመራጭ እንድትሆን ይተጋል!
image
image
image
image
image

በክፍለ ከተማው "የሥነ- ምግባርና የሞራል ዕድገት ለሀገር ህልውና" በሚል መሪ ሃሳብ ከወጣቶች ጋር ውይይት መድረክ ተካሄደ።

ታህሳስ 4, 2018
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ "የሥነ- ምግባርና የሞራል ዕድገት ለሀገር ህልውና" በሚል መሪ ሃሳብ ከወጣቶች ጋር ውይይት መድረክ ተካሂዷል። የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ከወጣቶች ክንፍ፣ ከወጣቶች ማህበር እና ሰላምና ፀጥታ ጽ/ቤት ጋር በጋራ በተዘጋጀው መድረክ ላይ ከሁሉም ወረዳዎች ለተውጣጡ ወጣቶች በሰላም እሴት ግንባታ ዙሪያ መነሻ ሰነድ ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል። የክፍለ ከተማው ብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ መብራቱ ደሴ ውይይቱ ወጣቶችን የሰላም ግንባታ ዋነኛ አካል አድርጎ በማሳተፍ ረገድ ጉልህ ሚና እንዳለው ጠቁመው በወጣትነት ዕድሜ ክልል ያሉ ዜጎች ጊዜያቸውን በአግባቡ በመጠቀም ለሃገር ልማት ጠንክረው ማስራት እንደሚጠበቅባቸው ተናግረዋል። አቶ መብራቱ አክለውም ወጣቶች ስራ ሳያማርጡ በተገኘው የስራ ፀጋ ላይ ተሰማርተው ከራሳቸውም አልፈው ለሌላው ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ሊሰሩ ይገባል ብለዋል። የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጀ ድሪብሳ ሀገርን ለማስቀጠል ተተኪ ወጣት ትልቁ ሚና እንዳለው ጠቁመው ወጣቱ ሙያዊ ስልጠናዎችን ወስዶ በአገር ግንባታ ላይ ንቁ ተሳታፊ በመሆን ሃገራዊ ኃላፊነቱን መወጣት እንደ አለበት ተናግረዋል። የክፍለ ከተማው ወጣቶችና ስፖርት ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ሙባረክ ደሊል፣ ወጣቶች በሰላም እሴት ግንባታ መጎልበት ዙሪያ ያላቸው ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀው የሰላም ግንባታ ጥረቶችን በማጠናከር ረገድ ሃላፊነታቸውን መወጣት እንዳለባቸው ተናግረዋል።

መልዕክትዎን ይላኩ

ሌሎች ዜናዎች