Welcome to Nifas Silk Lafto Subcity Peace and Security Office!       እንኳን ወደ ንፋስ ስልክ ላፍቶ ክ/ከተማ የሰላምና ጸጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በሰላም መጡ!       ጽ/ቤቱ ክ/ከተማችን በህዝብ ተሳትፎና ባለቤትነት ሰላምና ጸጥታ የሰፈነባት፤ የህግ የበላይነት የተረጋገጠባት ለኑሮ፣ ለስራ እና ለመዝናኛ ተመራጭ እንድትሆን ይተጋል!
image
image
image
image
image

የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በደንብ ቁጥር 156/2016 ዙሪያ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጠ።

መስከረም 3, 2018
ላፍቶ፣ ነሃሴ 2/2017:- የንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት በደንብ ቁጥር 156/2016 ዙሪያ ለዘርፉ የክፍለ ከተማና የወረዳ አመራርና ባለሙያዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል። የግንዛቤ መድረኩ ዋና ዓላማ ተቋሙ ቀጣይ ለሚያከናውነው የሰራተኛ ሪፎርም ሰራተኛው በቂ እውቀት እንዲኖረው የሚያስችል ነው ተብሏል። በዕለቱ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የክፍለ ከተማው ሰላምና ፀጥታ አስተዳደር ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ ደረጄ ዲሪብሳ ሪፎርሙ በዋናነት ክፍት የሆኑ የስራ መደቦች በሰው ኃይል እንዲሟሉና ባለሙያውሞ በባህሪና በክህሎት ብቃቱ ተመዝኖ ተቋማዊ ውጤታማነት እንዲረጋገጥ የሚያስችል ነው ብለዋል። በተጨማሪም ለስራ እንቅፋት የሆኑ ደንቦችና መመሪያዎችን በማስተካከል ተቋሙ በቴክኖሎጂ በመዘመን የተገልጋዮችን የአገልግሎት እርካታን ለመጨመር ፋይዳው የጎላ መሆኑን አንስተው ሰራተኛው በደንብና በመመሪያዎቹ ዙሪያ ተገቢውን ግንዛቤ በመያዝ በአፈፃፀም ሂደት ከሚኖሩ ብዥታዎች ነፃ ሊሆን እንደሚገባ ተናግረዋል። በማጠቃልያውም ስለ ሰራተኞች ድልድል መመሪያ ለተነሱ ጥያቄዎችና ሀሳቦች ግልፀኝነት መፍጠር ተችሏል።

መልዕክትዎን ይላኩ